በፋሲካ በዓል ሰሞን የአዲስ አበባን ብሎም የኢትዮጵያን ህዝብ ሲያነጋግር የነበረው የካሚላት ጉዳይ ከትናንት ወዲያ እልባት አገኘ የሚል ዜና ሰማሁ። በበቀል ወይም በቅናት በወጣቷ ላይ አሲድ በመድፋት የተከሰሰው የቀድሞ ፍቅረኛ ፣ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ሆኖ ስላገኘው በሞት እንዲቀጣ ፈርዶበታል። የሴቶች መበደል በመላው ዓለም ያለ ነገር ቢሆንም በሦስተኛው ዓለም ሀገሮች ደግሞ ጠንከር ብሎ ይታያል። ካሚላት ግፍ ከተፈፀመባቸው ብዙ ሴቶች መሀከል አንዷ ናት። በየጓዳው ብዙ በደል የደረሰባቸው ፣ በዝምታ ህይወታቸውንና መብታቸውን ያጡ ሴቶች አሉ። እንዲህ ዓይነቱን ነገር እንዲያደርስባት ያደረገችው የትኛውም ዓይነት በደል ቢሆን እንደማይገባት አምናለሁ ፤ ነገር ግን የፍርድ ቤቱ ህግ ትንሽ የበዛ መሰለኝ ስለህግ ብዙም ባላውቅም። የፍርዱ ውሳኔ ተገቢ ነው ወይስ ....።